"ጠብን፣ መቀየምን ትፈራለች፤ ፍቅርን፣ ሰው ማክበርን ትወዳለች። በእምነቷም፣ በልጆቿም በትዳሯም ጠንካራ ነበረች።" የወ/ሮ ወርቅነሽ ባለቤት አቶ አብርሃም ተዘራ ገሠሠ

W Beza.png

The late Worknesh Tlahun Kassa (Beza) 1983 - 2026. Credit: AT.Gessese

ወ/ሮ ወርቅነሽ ጥላሁን ካሳ (ቤዛ) ለሶስት ዓመታት ከማኅፀን ካንሰር ጋር ያካሔዱት ፍልሚያ አክትሞ ከእዚህ ዓለም በሕልፈተ ሕይወት ተለይተዋል። ባለቤታቸው አቶ አብርሃም ተዘራ፣ የቤተሰባቸው ወዳጅ አቶ ፍቅሬ (ራያ) ረታ እና የንስሃ አባታቸው መልአከ ፅዮን ቀሲስ እንግዳ ችሩ፤ የሜልበርን መካነ ሰላም ልደታ ለማርያም ወገብርኤል አስተዳዳሪ፤ የወ/ሮ ወርቅነሽን የሕይወት ዘመን አንስተው፤ ጥልቅ ሐዘናቸውን በመግለፅ ይዘክራሉ። የወ/ሮ ወርቅነሽ ጥላሁን ካሳ (ቤዛ) የቀብር ሥነ ሥርዓት ቅዳሜ ማርች 28 ቀን 2026 / መጋቢት 19 ቀን 2018 በወረቢ ቤተ መቃብር Corner Cemetery Rd & Railway Avenue 10:00 am ይፈፀማል።


አንኳሮች
  • ከልጅነት እስከ ዕውቀት
  • ከወሎ - መቀሌ
  • ከመቀሌ - ወሎ
  • ከኢትዮጵያ እስከ አውስትራሊያ
  • ሕልፈተ ሕይወት
  • ዝክረ መታሰቢያ
  • ምስጋና
ትሁት፣ ቀናና ለልጆቿ፤ ለባለቤቷ ፍቅርን የምትለግስ ናት። ለእሷ ስላለኝ ፍቅር፤ ለእሷ ያለኝን አክብሮት ለመግለፅ ቃላት ያጥረኛል። እሷ እንደዚያ ናት።
የወ/ሮ ወርቅነሽ ጥላሁን ባለቤት አቶ አብርሃም ተዘራ
ወርቅነሽ፤ ትሁት ልጅ ነበረች። ጥሩ ልጅ ነበረች። ለባሏ አሳቢ ነበረች። ከሰው ጋር ተግባቢ፤ ጥሩ ባሕርይ ያላት ነበረች።
የወ/ሮ ወርቅነሽ ቤተሰብ የቅርብ ወዳጅ አቶ ፍቅሬ (ራያ) ረታ
እህታችን ወ/ሮ ወርቅነሽ ፀዳለ ማርያም፤ እግዚአብሔርን ፈሪ፣ ቤተክርስቲያን አዘውታሪ፣ በቅዱስ ስጋው፣ በክቡር ደሙ፣ በንስሃ የኖረች፤ እጅግ በጣም ቅን ሰው ነበረች። እግዚአብሔር ዕረፍተ ነፍስ ያድልልን። ለልጆቿ፤ በጥበብ፣ በሞገስ፣ በሃይማኖት ማደግን ያድልልን። ባለቤቷን ያፅናናልን።
መልአከ ፅዮን ቀሲስ እንግዳ ቸሩ፤ የሜልበርን መካነ ሰላም ልደታ ለማርያም ወገብርኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪና የወ/ሮ ወርቅነሽ የንስሃ አባት

Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now