በጀመርነው ወር መባቻ ጁላይ 1 ቀን 2020 በአባይ ወሃ ላይ ፍትሃዊ አጠቃቀም ይኑር በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ ድርጅት ለሰብአዊ መብቶች ይፋው ድብዳቤን ለአፍሪካ ህብረት ጽፏል ፡፡ በአባይ ላይ የሚደረግ ማንኛውም አይነት ድርድር በአፍሪካ ህብረት መታየቱ ለሁሉም አገራት የተሻላ አማራጭ መሆኑንም የኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ ድርጅት ለሰብአዊ መብቶች ሰብሳቢ አቶ አቡላ አጉዋ እና አቶ ሰለሞን ከበደ የኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ ድርጅት ለሰብአዊ መብቶች ጸሃፊ አሳስበዋል፡፡
በአባይ ወሃ ላይ ፍትሃዊ አጠቃቀም ይኑር በሚል መርህ ለአፍሪካ ህብረት የተጻፈ ይፋዊ ድብዳቤ

LR-Ato Abulla and Ato Solomon Source: Supplied
“ በአድዋ ላይ ያስመዘግብነውን ድል በአባይ ላይ መድገም ይኖርብናል” - አቶ አቡላ አጉዋ “ አባይን እንደቀላል አንየው ለአትዮጵያ እድገት መሰረት ነውና ” - አቶ ሰለሞን ከበደ
Share




