ዶ/ር ግርማ አውጉቸው ደመቀ " የኢትዮጵያ ከፑንት እስከ 21ኛው ክፍል ዘመን መጀመሪያ " መጽሐፍ አርታኢ ፤ መጽሐፉ 16 የተለያዩ ቃለ ምልልሶችን እና 10 መጣጥፎችን ያካተተ ነው ብለዋል። ቃለ- ምልልሶቹ በኤስ ቢ ኤስ ራድዮ የአማርኛ ቋንቋ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ካሳሁን ሰቦቃ ፤ ከዳእማት እስከ ኢህአዲግ በሚል ርእስ ተዘጋጅተው በጣቢያው በተከታታይ የተላልፉ ናቸው። እንዲሁም አስሩ መጣጥፎች በተለያዩ ጸሀፊዎች ታሪክን ፤ ባህልን ፤ ኪነጥበብን እና ቋንቁን መሰረት አድርገው የተጻፉ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል ::
አንኳሮች
- ቃለ- ምልልሶች- ከዳእማት እስከ ኢሕአዲግ
- የምርምር እና የጥናት ጽሁፎች
- የአርታኢው ድርሻ
- ምስጋና
Share






