"ከኢትዮጵያ የመጣው አብዛኛው የአውስትራሊያ ነዋሪ በአንፃራዊ መልኩ በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ የሚገኝ በመሆኑ የሩስያና ዩክሬን ጦርነት አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድርበታል ብዬ አምናለሁ" ዶ/ር ደሴ ታርቆ

Community

Source: Getty

"የሩስያና የዩክሬይን ጦርነት የፈጠረው የቀውስ አጋጣሚ ኢትዮጵያውያን የተፈጥሮ ሃብታችንን እንድንጠቀምና ምርታማነት ላይ እንድንሠራ የምናስብበት ጊዜ ይመስለኛል። የኢትዮጵያ መንግሥት የኑሮ ውድነቱን ለማርገብ የሚችለው ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር ተነጋግሮ ድጎማ የሚያግኝበትንና ምርት በርካሽ ከውጭ ገበያ የሚያገዛበትን አማራጮች ሲፈልግ ነው" ዶ/ር ዮናታን ድንቁ


ዶ/ር ዮናታን ድንቁ - በአውስትራሊያ ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት ተመራማሪ እና ዶ/ር ደሴ ታርቆ አምባው - በደቡብ አውስትራሊያ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ንግድ ተመራማሪና መምህር፤ የዩክሬይንና ሩስያን ጦርነት ተከትሎ የግጭቱ መቀስቀስና በሩስያ ላይ የተጣሉ ዘርፈ ብዙ ማዕቀቦች ለዋጋ ግሽበት አስባብ ሆነው በተለይ በአውስትራሊያ፣ ኢትዮጵያና አፍሪካ ላይ ስላሳደሯቸው የኑሮ ውድነቶች ያስረዳሉ። 

አንኳሮች


 

  • የዋጋ ግሽበት ምንነትና መንስኤዎች
  • የኑሮ ውድነትና የዝቅተኛ ገቢ ተዳዳሪዎች
  • የኑሮ ውድነት በአውስትራሊያ

Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now