ፈቃዱ ዲኖ፤ መፅሐፍ ሻጩና የኑሮ ትንቅንቅ በአዲስ አበባ

Fekadu Dino. Source: SBS Amharic
ፈቃዱ ዲኖ፤ በቅርቡ ከሱቅ በደረቴ መፅሐፍት አዟሪነት ወደ ባለ አንዲት መደርደሪያ መፅሐፍት ሻጭነት የዞረ ታታሪ ነው። ባለ ትዳርና የዘጠኝ ዓመት ወንድ ልጅ አባት ነው። ባለቤቱ በመንግሥት ድጎማ በወር 1400 ብር ታገኛለች። ፈቃዱ በለስ የቀናው ዕለት 200 ብር አትርፎ ይውላል። አንዲትም መፅሐፍ ሳይሸጥ የሚውልባቸው ቀናትም አሉ። ከቤተሰቡ ጋር የአዲስ አበባን ኑሮ ውድነት የሚገፋው እንዲያ ነው። ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ ስለሆነ "ቁጠባ"ን ከቃልነቱ ባሻገር ንዋይ ሆኖ የባንክ ደብተሩ ላይ ሠፍሮ አይቶ አያውቅም። እንዲያም ሆኖ እንደምን ቤተሰቡንና ደካማ እናቱን እያገዘ "እንደሚኖር" ያወጋል።
Share