አቶ ግዛቸው ቀዲዳ - የኢትዮጵያ የሕክምና ላቦራቶሪ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር፤ ግማሽ ክፍለ ዘመን ስላሸመገለው ማኅበር፣ የኢትዮጵያን የሕክምና ላቦራቶሪ አገልግሎት ዕድገት ደረጃ፣ ተግዳሮቶችና አስተዋፅዖዎች አስመልክተው ይናገራሉ። "በዓለም አቀፍ ደረጃ የላቦራቶሪ አገልግሎቶች ከ3500 - 4000 የላቦራቶሪ ምርመራ ዓይነቶች ሲካሔዱ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በመንግሥት ጤና አገልግሎቶች የሚሰጡት ምርመራዎች 50ም ቢሞሉ ጥሩ ነው። በግል ድርጅቶች ምናልባትም 100 ያህል ሊደርሱ ይችላሉ" በማለት ክፍተቶችን ያመላክታሉ።
አንኳሮች
- የኢትዮጵያ ሕክምና ላቦራቶሪ ማኅበር ምሥረታ፣ ዓላማና ሚና
- የኢትዮጵያ ላቦራቶሪ ባለሙያዎች የስልጠና ልህቀት ደረጃ
- የላቦራቶሪ አገልግሎት ተገቢ ሥፍራ መነፈግና መዘዞቹ
Share






