አቶ ሞገስ ከልክሌ የHorn of Africa Insight ድረገጽ መሥራችና ዋና አዘጋጅ፤ አቶ ዮሴፍ አንተነህ የHorn of Africa Insight መሥራችና አባል፤ የሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት በኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን መካከል በሚካሄዱት ቀጣይ ድርድሮች ላይ ስለሚኖረው ሚና ይናገራሉ። አቶ ሞገስ “ስትራቴጂያዊ ጥያቄው ኢትዮጵያ ዓባይ ወንዝ ላይ መጠቀም ትጀምራለች ወይ የሚለው ነው” ሲሉ፤ አቶ ዮሴፍ “ኢትዮጵያ በገዛ ወንዟ ሳትጠቀም ሌላውን እየጠቀመች መኖር አትችልም” ይላሉ።
Share






