ግርማ ይፍራሸዋ ኢትዮጵያ ስመጥር የፒያኖ ተጫዋችና ሙዚቃ ቀማሪዎች አንዱ ነው። ከያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት እስከ ሶፊያ ስቴት የሙዚቃ አካዳሚ ዘልቆ በአገርኛና የምዕራባዊያን ረቂቅ ሙዚቃ ተጠብቧል።
አንኳሮች
- ውልደትና ዕድገት
- ከሙዚቃ ጋር ፍቅር ላይ መውደቅ
- ከክራር እስከ ፒያኖ
ግርማ ይፍራሸዋ ከክራር እስከ ፒያኖ፤ ከያሬድ እስከ ባኽ፣ ሞዛርትና ቢትሆቨን ግዘፍ ነስተው በአፍሪካ፣ አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ መድረኮች ላይ ናኝተዋል።
በመጪው ወርኅ ኖቬምበር በሜልበርን - አገረ አውስትራሊያ "The Spirit of the Nile" በሚል መጠሪያ ሶስት መድረኮች ተሰናድተውለታል።

እንደ አውስትራሊያውያኑ ሁሉ ኢትዮጵያውያኑም ታድመው ምሽችን በጋራ በጥበብ ሥራው በሐሴት ሊመሉ ይጠብቁታል።
ግርማም መሰናዶውን ከውኖ ታዳሚዎቹን በምዕራባውያኑና አገርኛ ረቂቅ የፒያኖ ጥበብ ሥራዎቹ ከመድረክ እነሆኝ ለማለት ዝግጁ ሆኗል።
Share






