ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም - የቀድሞው የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኅብረት (ኢዲኅ) መሥራችና መሪ፤ ስለ ድርጅታቸው ምሥረታና ፖለቲካዊ ሚና ይናገራሉ። ከኢሕአዴግ ሽግግር መንግሥት እንደምን እንደተባረሩ ሲገልጡም “ለኤርትራ ነፃነት ዕውቅና ተጠይቀን የለም የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝብ ነው መነጋገር ያለበት እንጂ በሽግግር መንግሥት ደረጃ መቀበል ያስቸግረናል፤ ተገቢም አይደለም በሚል ተቃወምን። እንግዲያ ወንበራችሁን አስረክቡ ተብለን አስረከብን” ይላሉ። ዳግም የቀረበ።
አንኳሮች
- የፀረ ደርግ የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ
- ከሱዳን በረሃ እስከ ኢሕ አዴግ የሽግግር መንግሥት ፓርላማ አባልነት
- ከፖለቲካ ዓለም ስንብት
Share






