ወ/ሮ ትዕግስት ከበደ - የሐበሻቪው ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፤ ከኦክቶበር 14-16, 2022 / ጥቅምት 4 - 6, 2015 ድረስ በአገረ እንግሊዝ ለንደን ከተማ ስለሚካሒደው የኢትዮጵያ ፊልም ሳምንት ይናገራሉ። በሶስቱ ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ስለሚቀርቡት ሲመት፣ ሂሩት አባቷ ማን ነው? እና ርዕስ ፍለጋ ስለተሰኙት ሶስት ፊልሞች ይዘትና ታሪካዊ ፋይዳዎቻቸውን አስመልክተው ያስረዳሉ።
አንኳሮች
- የኢትዮጵያ ፊልሞች ዓለም አቀፍ መድረኮችን የማግኘት ፋይዳዎች
- የፊልም መረጣ ሂደቶች
- የሐበሻቪው የዕይታ አቅርቦት ዘርፎች
Share






