ዳባሳ ዋቅጅራ፤ ከጥቁር እንጪኒ እስከ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን

Community

Dabassa Waqjira. Source: D.Waqjira

አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ የሜልበርን - አውስትራሊያ ነዋሪ ናቸው። ከዚያ በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛና እሥረኛ፣ በአገረ ኬንያ ስደተኛ ነበሩ። የሕይወት ጉዟቸው መነሻ የቤተሰባቸው ስምንተኛ ልጅ ሆነው ለውልደት የበቁባት ጥቁር እንጪኒ ናት።


የፊደል ገበታ

አቶ ዳባሳ ፊደል መቁጠር የጀመሩት ዘግይተው ነው። ሆኖም ከክፍል ክፍል ቀልጥፈው በመሸጋገር የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቅቀዋል።

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የፈፀሙት የኢሕዲሪ (ደርግ) ሥርዓት በኢሕአዴግ ተተክቶ ሳለ ነው። 

በዚያም አላበቁም ከጅማ እርሻ ኮሌጅ በእርሻ ትምህርት በዲፕሎማ ተመርቀዋል።
Community
Dabessa and his freinds in Jimma Agricultural College - 1993 (F-L). Source: D.Waqjira
የሥራ ዓለም  

በወቅቱ በቁቤ አፋን ኦሮሞ ሰልጥነው ነበርና ክህሎታቸው ለአስተማሪነት፣ ሲልም ለማዘጋጃ ቤት ተቀጣሪነት አብቅቷቸዋል።

የማዘጋጃ ቤት ሠራተኛ ሆነው ሳለ እ.አ.አ በ1994 የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሥራ ማስታወቂያ አወጣ። 

አመለከቱ። ተወዳድረውም አለፉ።

የኮሌጅ ትምህርታቸው ዋቤ ሆኗቸው በኦሮምኛ ዝግጅት ክፍል ለእርሻ ጋዜጠኛነት በቁ።

በእርሻ ሪፖርተርነት ሳይወሰኑ የሁሉም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቋንቋ ማዕከል አስተባባሪ እርክን ላይ ደረሱ።

ሥራቸው ላይ እያሉ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘልቀው የጋዜጠኛነት ሙያ ዕውቀት ቀሰሙ።
Community
Graduation ceremony at Addis Ababa University - 1998. Source: D.Waqjira


 

 

   

 


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service