አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ ከሶስት ልጆቻቸው ጋር አውስትራሊያ ዘልቀው ሳይረጋጉ ባለቤታቸው ላይ የ10 ዓመት እሥር ብይን መጣሉን ሰሙ። በጠበቆቻቸው አማካይነት ይግባኝ አሉ። በለስ ቀናቸው። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ክሱን ውድቅ አደረገ። ባለቤታቸው ከሶስት ዓመታት እሥራት በኋላ በነፃ ተለቀቁ። ሁለት ዓመታት ቆይተው አውስትራሊያ እንዲሠፍሩ ይሁንታን አገኙ። ባልና ሚስት ከተለያዩ ከዘጠኝ ዓመታት በኋላ ዳግም በአንድ ጣራ ስር መኖር ጀመሩ።
ባልና ሚስቱ አንድ አልጋ መጋራት በጀመሩ በዓመቱ አንድ ልጅ አፈሩ።
በአሁኑ ወቅት የመጀመሪያ ትልቋ ልጃቸው ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ሥራ ላይ ተሠማርታ ትገኛለች።
ሁለተኛ ልጃቸውና ሶስተኛ ልጆቻቸው የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ላይ ይገኛሉ።
የአውስትራሊያ ፍሬ የሆነችው የመጨረሻ ልጃቸው የሁለተኛ ክፍል ተማሪ ናት።
Share






