ወ/ሮ ማሜ ወርቁ - በዩናይትድ ስቴትስ ዌስት ኮስት የሕዝባዊ ዲፕሎማሲ ሰብሳቢ፣ ዶ/ር ዑስማኢል ጎርሴ - የኢትዮጵያ ሶማሌ ዲሞክራሲያዊ ፎረም ሊቀመንበርና ደጀን የማነ - በኒው ሳውዝ ዌይልስ ዩኒቨርሲቲ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ሶስተኛ ዲግሪ ተማሪ፤ በኢትዮጵያ መንግሥት የተናጠል ተኩስ ማቆም ዕወጃና ለትግራይ ቀውስ ሰላማዊ መፍትሔ ፍለጋ ሂደት ላይ አተያያቸውን ያንጸባርቃሉ።
አማራጭ መፍትሔዎች
- የኢትዮጵያ መንግሥትም ሕወሓትም ጦርነት ያቆሙ
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሁሉም ባለድርሻዎች ጋር ተቀምጠው ይነጋገሩ
- ልዩነቶቻችንን በማጥበብ በጋራ በሚያስማሙን ጉዳዮች ላይ እናተኩር
- ዶ/ር ዑስማኢል ጎርሴ

- ንግግር ሲባል የአንድ ወገን ብቻ ሆኖ መታየት የለበትም
- ፖለቲካዊም ሆነ ወታደራዊ አማራጮች መፍትሔ አይሆኑም
- ሉዓላዊነትን ለማስከበር ሲባል ማድረግ የማንሻው ቢሆን እንኳ ማድረግ ግድ የምንሰኘበትም ሁኔታ ሊኖር ይችላል
- ወ/ሮ ማሜ ወርቁ

- ጦርነት አማራጭ አይሆንም፤ ለሰላም የሚከፈል መስዋዕትነት ያስፈልጋል
- ሕገ መንግሥቱን የምንጠራ ከሆነ ሕገ መንግሥቱን እየጠራን፤ ታሪክም የምንጠራ ከሆነ ታሪክ እየጠራን ያሉንን ችግሮች እየጠራን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍታት መቻል አለብን
- እያንዳንዱ ክልል ሕዝበ ውሳኔ ማካሔድ አለበት
- ደጀን የማነ

Share






