ዶ/ር ተበጀ ሞላ - በዲከን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ተመራማሪ፣ ዶ/ር ላይችሉህ ባንቴ መኮንን - በደቡብ አውስትራሊያ ዩኒቨርሲቲ የመድኃኒት ግኝትና ቅመማ ጥናት ተመራማሪ፣ ኃይሌ አረፈዓይኔ - በሳውዘርን ክሮስ ዩኒቨርሲቲ የከርሰ ምድር ውኃና ማዕድን የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪና ጋዜጠኛ መሐመድ አባዋጂ ኢትዮጵያን ገጥመዋት ላሉት ችግሮች መንስዔዎች የሚሏቸውን ነቅሰው ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።
ለወቅታዊው የኢትዮጵያ ችግሮች መንስዔዎቹ ምንድናቸው?
- ስልጣን በለቀቀው አካል ሕወሓትና ኢትዮጵያን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማሸጋገር ራሱን ብልፅግና ብሎ በሚጠራው መካከል የተፈጠሩ ችግሮች ናቸው።
- ጋዜጠኛ መሐመድ አባዋጂ

- አሃዳዊነት - አንድ ቋንቋ፣ አንድ ሃይማኖት፣ አንድ ብሔር ለመመሥረት የሚካሄድበት መንገድ አሁን ወዳለንበት ደረጃ አድርሶናል።
- ኃይሌ አረፈዓይኔ

- አሁን ለደረሰው የሰብዓዊ ቀውስ፣ ዲፕሎማሲያዊ ቀውስና ፖለቲካዊ ቀውስ ምክንያቶቹ በሕዝብ ትግል የመጣን ለውጥ ለራሳቸውና ለቡድናቸው ያተኮሩ ቡድኖች ከሕዝብ ጠልፈው ለራሳቸው መውስዳቸው ነው።
- ዶ/ር ላይችሉህ ባንቴ መኮንን

- በመሃል አገር መንግሥትና በክልላዊ አስተዳደር መንግሥት የነበረ ቁርሾ፣ የዓባይ ግድብና ዓለም አቀፍ ኃይሎች የፈጠሩት ጫናዎች፣ የዘር ተኮር ጥቃቶችና የኢኮኖሚ ድቅቀት ለቀውስ አድርሶናል።
- ዶ/ር ተበጀ ሞላ

Share






