በተለይ የሴቶች ልዩ በዓል የሆነው ሀገር በቀሉ የአሸንዳ ክብረ በዓል በሜልበርን አውስትራሊያ ቅዳሜ ነሐሴ 17 / ኦገስት 23 በትግራይ ማኅበረሰብ አባላት ዘንድ በሐሴት ተመልቶ፤ በድምቀት ተከብሮ ውሏል። በቪክቶሪያ የትግራይ ሴቶች ማኅበር አመራር አባላትና የበዓሉ ተሳታፊዎች የአሸንዳ በዓል ስሜቶቻቸውን ገልጠዋል፤ ለመላ ኢትዮጵያውያንም የመልካም ምኞት መልዕክቶቻቸውን አስተላልፈዋል።
አንኳሮች
- የአሸንዳ ትሩፋቶች
- ሴቶችና አሸንዳ
- የመልካም ምኞት መልዕክቶች
Share






