የኢትዮጵያ መንግሥት የተናጠል ተኩስ ማቆም ዕወጃ ፋይዳ ምንድነው?

Ambulances of Red Cross are seen at the Mekele General Hospital in Mekele, on June 24, 2021.

Ambulances of Red Cross at Mekelle General Hospital in Mekele, on June 24, 2021. Source: Getty

ዶ/ር ፍሳሃ ኃይለ ተስፋይ በዲከን ዩኒቨርሲቲ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ተመራማሪ፣ አቶ አዳሙ ተፈራ የቀድሞው የቪክቶሪያ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንትና አቶ አያሌው ሁንዴሳ የቀድሞው የኒው ሳውዝ ዌይልስ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ በኢትዮጵያ መንግሥት የተናጠል ተኩስ ማቆም እወጃና ሰላማዊ መፍትሔ ፍለጋ ሂደት ላይ አተያያቸውን ያንጸባርቃሉ።


ተኩስ አቁም

“የረጅም ጊዜ አዎንታዊ ተፅዕኖው ወደፊት የሚታይ ሆኖ፤ መንግሥት የወሰደውን የአንድ ወገን ተኩስ አቁም የምመለከተው በአዎንታዊ ጎኑ ነው። የመንግሥትን ሆደ ሰፊነትና ቻይነት የሚያሳይ መልካም ራዕይ ያለው ውሳኔ ነው።” አቶ አዳሙ ተፈራ
Adamu Tefera.
Adamu Tefera. Source: A.Tefera
“የፌዴራል መንግሥቱ ተኩስ አቁሜያለሁ ብሎ ቢያውጅም፤ የእርዳታ ክልከላው፣ የቴሌኮም ክልከላው፣ ድልድይ መስበሩና ባንክ እንዳይንቀሳቀስ ማድረጉ አልቆመም። ጦርነቱ መልኩን ቀየረ እንጂ የፌዴራል መንግሥቱ ጦርነቱን አስቁሞታል የሚል ዕምነት የለኝም።” ዶ/ር ፍሳሃ ኃይለ ተስፋይ
Dr Fisaha Haile Tesfay.
Dr Fisaha Haile Tesfay. Source: FH.Tesfay
“የተወሰደው የተኩስ ማቆም ሰከን ብለን ከዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት እንወጣለን ብሎ ለማሰብና ወደ ፖለቲካዊ መፍትሔ ለመሔድ ዕድል ይሰጣል ብዬ አስባለሁ።” አቶ አያሌው ሁንዴሳ
Ayalew Hundessa.
Ayalew Hundessa. Source: A.Hundessa
ሰላማዊ መፍትሔ

“ሰላም ለማምጣት ከተፈለገ መሪዎች በቀጥታ መነጋገር አለባቸው። ወደዚያ የሚያሸጋግሩ የተመቻቹ ሁኔታዎች መፈጠር አለባቸው። አገራዊ መፍትሔ መፈለግ አለበት።” አቶ አዳሙ ተፈራ

 

“በጦርነት በፍጹም የትም አይደረሰም። የሰላም ድርድሩ የእውነት ከሆነ፤ አገሪቷ አሁን ካለችበት ምስቅልቅል ሁኔታ ወጥታ እንድትገኝ የምንፈልግ ከሆነ የፌዴራል መንግሥቱ ወይም የዐቢይ መንግሥት ላይ ተፅ ዕኖ ማሳደር ያስፈልጋል።”  ዶ/ር ፍሳሃ ኃይለ ተስፋይ


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service