"የዳያስፖራ ባንክ አገልግሎት ክፍል ዓላማ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ፍላጎቶችና የባንኩን አቅርቦቶች በማያያዝ ለማገልገል ነው"አቶ ዘሪሁን ተከተል

Zerihun Teketel CBE.png

Zerihun Teketel, Manager of the Ethiopian Diaspora Banking Unit at the Commercial Bank of Ethiopia, and the headquarters of the Commercial Bank of Ethiopia, centre, and skyscraper offices in Addis Ababa, Ethiopia, on Wednesday, 19 October 2022. Credit: Amanuel Sileshi/Bloomberg via Getty Images / Z.Teketel

አቶ ዘሪሁን ተከተል፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳያስፖራ ባንክ ክፍል ሥራ አስኪያጅ፤ ሰሞኑን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት መካከል የተካሔደውን የመግባቢያ ሰነድ ፍረማ ፋይዳዎችን አንስተው ያስረዳሉ።


አንኳሮች
  • የመኖሪያ ቤት፣ የንግድ፣ የመኪናና የፕሮጄክቶች ብድር አሠራር
  • የወለድ መጠኖች
  • የባንክ ሂሳብ አከፋፈት
  • የባንክ ሂሳብ ዓይነቶች
ዳያስፖራ ብለን የምናጠቃልላቸው ኢትዮጵያዊ ሆነው በውጭ የሚኖሩ፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሆነው የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸውንና በውጭ ሀገር አንድ ዓመትና ከእዚያ በላይ ኖረው የተመለሱትን ነው።
አቶ ዘሪሁን ተከተል፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳያስፖራ ባንክ ክፍል ሥራ አስኪያጅ
በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን 'ሀገሬ ላይ ቤት ልግዛ ወይም ልሥራ ወይም የተጀመረ ቤት ልጨርስ' ብለው ለሚያስቡ፤ ዝቅተኛው 10 በመቶ የሆነ መዋጮ በማውጣት እስከ 20 ዓመት የሚቆይ ባለ ሶስት ዘርፍ ብድር ተዘጋጅቶላቸዋል።
አቶ ዘሪሁን ተከተል፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳያስፖራ ባንክ ክፍል ሥራ አስኪያጅ
በውጭ ምንዛሪ በባንክ ሂሳብ የተቀመጠው፤ ሀገር ውስጥ በዶላር ወጪ አይደረግም። በብር ይቻላል። ለምን? ኢትዮጵያ ውስጥ የገንዘብ ዝውውር በብር ስለሆነ ነው። እሱን እናጥራ። ነገር ግን፤ ውጭ ሆነው በዶላር የገንዘብ ዝውውር ማድረግ የሚፈልጉ የእራሳቸውን የባንክ ሂሳብ በዶላር መጠቀም ይችላሉ።
አቶ ዘሪሁን ተከተል፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳያስፖራ ባንክ ክፍል ሥራ አስኪያጅ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት መካከል የተካሔደው የመግባቢያ ሰነድ ፊርማ፤ አግልግሎቶችን ለዳያስፖራው ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ነው።
አቶ ዘሪሁን ተከተል፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳያስፖራ ባንክ ክፍል ሥራ አስኪያጅ

Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now