የውይይት መድረክ፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ከየት ተነስቶ የት ደርሷል?

Eth Logo.png

Credit: ECAV

ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር፣ ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ፣ አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚና ቦርድ አባል፣ ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ በቀዳሚ የመወያያ አጀንዳነት በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር የ38 ዓመታት ጉዞ በከፊል ነቅሰው ግለ አተያያያቸውን ያጋራሉ።


አንኳሮች
  • ትሩፋቶች
  • ፋይዳዎች
  • የአገልግሎት ጉዞ

የማኅበሩ አንዱ ትልቁ ውለታ ሳይከስም ይህን ያህል ጊዜ መሔዱና በርካታ ሥራዎችን መሥራቱ ነው፤ ማኅበሩ በማደግ ላይ ሳይሆን ባለበት እያዘገመ ነው ያለው።
ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት
የማኅበሩ ጥቅምና ጉዳቱ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ጥሩ ደረጃ ላይ የደረሰበትም ጊዜ ነበር፤ እንደ አመሠራረቱ ብዙም ደረጃ ላይ አልደረሰም። በጣም የተለየ ሥራ ሠርቷል ብዬ የማስበው 23 ገፆች ያሉት መተዳደሪያ ደንብ ማፅደቁ ነው።
አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ
ወደ ላይ ጥሩ ቦታ ደርሰን፤ ወደ ታች የወረድንበት ሁኔታ አለ።
አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚና ቦርድ አባል
የማኅበሩ ድክመት እንዳለ ሆኖ፤ የኢትዮጵያዊነት ወግና ባሕልን በመጠበቅ፣ በስፖርት፣ የአዲስ ዓመትንና ሌሎችንም ሥራዎች ሲሠራ የቆየ ነው።
ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤
ችግሮች እንዳሉ ይታወቃል። የጎላ እንቅስቃሴ ባይኖረውም፤ ማኅበሩ ጠፍቷል፤ የለም ማለት አይቻልም። አንድ ማኅበረሰብ የሚጠናከረው አመራርና ፖሊስ ሲኖረውና ያንንም ተንተርሶ ሲሠራ ነው። በእርግጥ ማኅበሩ ያንን ተንተርሶ እየሠራ ነው ወይ?
ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር

Share

Recommended for you

Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service