የፊልም ጥበብ ነፃ የተምህርት ዕድላቸውን ናይሮቢ ኬንያ ያጠናቀቁት ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሔኖክ ተሾመና ሃብታሙ መኮንን፤ የትምህርት ዕድሉ እንደምን ለዓለም አቀፍ መድረክ እንዳበቃቸውና ግባቸውን ከአገር ቤትና ከአኅጉር አሻግረው ሉላዊ እንዳደረጉ ይገልጣሉ። በኬንያ ቆይታቸው ባይተዋርነት ሳይሆን ቤተሰባዊ ስሜት እንዲሰማቸው ላደረጓቸው የኬንያ ነዋሪ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላትንና በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲን ያመሰግናሉ።
አንኳሮች
- ነፃ የትምህርት ዕድል
- ድንበር አልባ የፊልም ፕሮጄክት ውጥን
- የማኅበረሰብና የኤምባሲ ድጋፍ
Share





