ሮዛ ገብረመስቀልና መሠረት ይፍሩ፤ ቤይሩት - ሊባኖስ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በተጨማሪ ደርሰው ስላሉ ሥራ አጥነት፣ እንግልት፣ በቀድሞ አሠሪዎች ደጅ መጣል፣ ለዕለት ጉርስ መቸገር፣ ወደ አገር ቤት ሔዶ ዳግም ለሥራ አጥነት በመዳረግና ሊባኖስ ውስጥ ሆኖ ክፉ ቀንን የመግፋት አጣብቂኝ ውስጥ የመኖር ውዥቀትን አንስተው ይናገራሉ። በሜልበር - አውስትራሊያ ፓስተር ደሲ ባይሳ - የቤይሩት እህቶች ሚሽን አስተባባሪ የችሮታ ተማፅኖ ያቀርባሉ።
አንኳሮች
- ኢትዮጵያውያን በቤይሩት - ሊባኖስ
- የቤይሩት እህቶች ሚሽን
- የወገን - ለወገን ይድረስ ጥሪ
Share






