"የበጎ አድራጎት ተረጂ ወጣቶቻችን የትምህርትና የቴኒስ ሥልጠና እንዳይቋረጥብን የኢትዮጵያውያንን ሁለገብ እርዳታ እንሻለን" አቶ ታሪኩ ተስፋዬ

Community

Tariku Tesfaye. Source: T.Tesfaye

አቶ ታሪኩ ተስፋዬ - የታሪኩ ተስፋዬና ደስታ ተስፋዬ የሕፃናት ትምህርት የቴኒስ ዕድገት ማኅበር በጎ አድራጎት ድርጅት መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ናቸው። አቶ ታሪኩ ከወንድማቸው ጋር ሆነው ከቴኒስ ኳስ አቀባይነት ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ እስከ መወከል ደርሰዋል። አቶ ታሪኩ በዝነኛው ዴቪስ ካፕ፤ አቶ ደስታ በአፍሪካ ሻምፒዮና።


አቶ ተስፋዬና አቶ ደስታ እንደ አብዛኛው ኢትዮጵያውያን ሁሉ ከዝቅተኛ ኑሮ ነዋሪ ቤተሰብ የወጡ ናቸው።

ወላጆቻቸው አቅሙ ኖሯቸው ቀልባቸውን ለገዛውና ክፍያን ግድ ለሚለው የሜዳ ቴኒስ ንዋይ ባያፈሱላቸውም ወንድማማቾቹ ወጣቶች ግና በኳስ አቀባይነት ለቴኒስ ሜዳ ቅርብ ሆነው ራኬት ለመጨበጥ ቆይተዋል።

ያም አስባብ ሆኖ ረጂ አግኝተው፤ ጥረቶቻቸውን አክለው ሕልማቸው ጉም መጨበጥ ሆኖ እንዳይቀር አድርገዋል።

ሩጫና እግር ኳስ በገነነባት አገር ፕሮፌሽናል የቴኒስ ተጫዋቾች ለመሆን በቅተውም ባሕር ማዶ ተሻግረው ተወዳድረዋል። የአገራቸውን ኢትዮጵያ ስምም በዓለም አቀፍ መድረክ አስጠርተዋል።
Community
Tariku Tesfaye. Source: T.Tesfaye
ሁለቱ ወንማማቾች ማንነታቸውን ቸል ያሉ፤ አስተዳደጋቸውን የዘነጉ አልነበሩም። ሲልም "መስጠትን የማያውቅ፤ መቀበል ማን አስተማረው?" እንዳይሆን የከእጅ ወደ አፍ  ኑሮአቸው ወቅት በችሮታቸው በታደጓቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖች ሳቢያ ለባለሙያተኛነት እንደበቁ ሁሉ፤ ውለታ የሚገባቸው፤ መቀበልን ብቻ ሳይሆን መስጠንም የሚያውቁ መሆናቸውን በግብር ሊያውሉ ተነሱ። 

የታሪኩ ተስፋዬና ደስታ ተስፋዬ የሕፃናት ትምህርት የቴኒስ ዕድገት ማሕበር በጎ አድራጎት ድርጅትን በጋራ መሠረቱ። የተረጂ ረጂ ሆኑ። 

ባለፉት 20 ዓመታት ውስጥም 300 ኢትዮጵያውያን ሕፃናትን ለቴኒስ ተጫዋችነት አብቅተዋል። በቀለም ትምህርትም ዕውቀት አስቀስመዋል።

በስልጠና ያፈሯቸው ወጣት ቴኒስ ተጫዋቾች በአገር ውስጥና በውጭ አገራት በተለያዩ የዕድሜ ደረጃዎች ተሰልፈው በርካታ ድሎችን በመንሳት የ487 ዋንጫ ባለቤቶች ለመሆን በቅተዋል።

ከ500 በላይ የወርቅና የብር ሜዳሊያዎችን በአገር ውስጥ ውድድሮች ለአዲስ አበባ መስተዳድር፤ 68 የወርቅና የብር ሜዳሊያዎችን ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል። 

እኒህን ሁሉ ውጤቶችን በአገር ቤትና በባሕር ማዶ ያስገኙና ወደፊትም ለላቀ ውጤት አልመው ያሉ ልጆች በተስፋ ዓለም እንዳይቀሩባቸውም የኢትዮጵያውያን ረድኤት እንሻለን ይላሉ።  

      


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service