ዶ/ር በሪሁን መጋቢያው፤ በሞናሽ ዩኒቨርሲቲ የኅብረተሰብ ጤና ተቋም ተመራማሪና መምህር፣ በሜልበርን የቤተሰብ የሕክምና ሐኪምና የአዕምሮ ጤና ተመራማሪ የኮሮናቫይረስ ገደቦችና የአዕምሮ ጤና አስመልክቶ ሙያዊ አተያያቸውን ፤ ተማሪ ቴዎድሮስ ወርቁና ተማሪ ማኅተመ ሰለሞን የርቀት ትምህርት ተሞክሯቸውን ያጋራሉ።
"ወላጆች ልጆቻቸው የስነ ልቦና እርዳታ ሲያስፈልጋቸው ሳይዘገዩ ቀደም ብለው እርዳታ ሊጠይቁ ይገባል። በቋንቋቸው የስነ ልቦና እርዳታ ማግኘት ይችላሉ" ዶ/ር በሪሁን መጋቢያው

“የ8ኛ ክፍል ተማሪ ነኝ። የኦንላይን ትምህርት በጣም ያስቸግራል። ጓደኞቼን እናፍቃለሁ፤ ትምህርት ቤቴን እናፍቃለሁ” ተማሪ ቴዎድሮስ ወርቁ

“ቤት ውስጥ መቀመጥና የሕጉ መብዛት በተለይ ለልጆች በጣም ያስጨንቃል። ትምህርታችንን አቋርጦብናል” ተማሪ ማኅተመ ሰለሞን

Share






