"አባታችን ሃይማኖታችንን እንድንጠብቅ፣ ሰው እንድናከብር፣ አገራችንን እንድንወድ ቸርነትና በጎነትን ያጎናፀፈን ነው፤ እሱን ማጣት ትልቅ ጉዳት ነው" ኢንጂነር ሚካኤል ታደለ

Tadele Feleke. Credit: M.Tadele
በፐርዝ - ምዕራብ አውስትራሊያ ነዋሪ የነበሩትና ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የአቶ ታደለ ፈለቀ ቀብር ሥነ ሥር ዓት ዓርብ ዲሴምበር 29 / ታህሣሥ 19 ይፈፀማል። በፐርዝ ደብረ መድኃኒት መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ገሪማ "ታደለ ማለት ሀገር የሌለው፣ ብሔር የሌለው፤ የስደተኞች ተቀባይ፣ ለቤተክርስቲያን ሕይወቱን ያበረከተ ቅን አገልጋይ ነው። የኢትዮጵያ ምልክት ነው። 'መጋቢ ፍቅር ታደለ' ብለን የምንጠራው በሁሉም ዘንድ ተወዳጅ፣ አዛኝና ሩህሩህ በመሆኑ ነው" ሲሉ ገልጠዋቸዋል።
Share