የውይይት መድረክ፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር / የኢትዮጵያውያን ማኅበር በቪክቶሪያ የገጠሙት ተግዳሮቶችና ያስከተሏቸው መዘዞች

Panelists 1.png

Adamu Tefera (L), Dr Bichok Wan (LB), Ahmed Dawd (C), Taklo Teshome (RT), and Alemayehu Bezabih (RB). Credit: A.Tefera, B.Wan, A.Dawd, T.Teshome, and A.Bezabih

ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር፣ ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ፣ አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚና ቦርድ አባል፣ ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ በተከታይ የመወያያ አጀንዳነት በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር / የኢትዮጵያውያን ማኅበር በቪክቶሪያ የገጠሙትን ተግዳሮችና ያስከተሏቸውን መዘዞች አስመልክተው ግለ አተያያቸውን ያንፀባርቃሉ።


አንኳሮች
  • ተግዳሮቶች
  • መንስኤዎች
  • መዘዞች
የማኅበረሰብ አባላት ንቁ ተሳትፎ መጥፋት፣ የጎሳ ፖለቲካ፣ የቤተ ክርስቲያን ክፍፍል፣ የአመራር አባላት ክህሎትና ዲሲፕሊን ማነስ፣ ለቃሉ የሚያድርና ኃላፊነትን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ የሆነ ሰው ጥቂት መሆን፤ ማኅበሩን ከጎዱ ችግሮች ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው።
ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣
ማኅበሩን እንደራስ ጉልት ወይም ንብረት አድርጎ ማየት፣ የተለያዩ ቡድኖችን አሰባስቦ በማሳመፅ የተመረጡ ሰዎችን ማጥቃት፣ ብቃት የሌላቸውን ሰዎች መምረጥ፣ የብሔር ድርጅቶች መብዛት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማኅበሩን ለመቆጣጠር የሚያደርጉት ሩጫ ከፍተኛ ተግዳሮቶች ሆነው ለማኅበሩ መዳከም ምክንያት ሆነዋል።
አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ
ዋነኛ ችግሮቻችን፤ የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ በተግባር አለማዋል፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሰብዓዊ መብቶች ሲጣሱ ወደ ጎን ብሎ ማለፍና ለስፖርት ዋጋ አለመስጠት ናቸው።
አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር የቦርድ አባልና ሥራ አስፈፃሚ (ዕገዳ ላይ)
አንዱ ችግር የአመራር አባል በመሆን አንድ ነገር አገኝበታለሁ ብሎ መግባትና ያ ሳይገኝ ሲቀር መጥፋት ነው።
ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር
ተግዳሮቶቹ፤ የመተዳደሪያ ደንቡን አለመፈፀም፣ አምባገነንነትና ግለኝነት መንገሥ፣ የማኅበረሰብ ተሳትፎ አለመኖር፣ በዘር ፖለቲካ ምክንያት ማኅበሩን የኢትዮጵያውያን ብሎ አቅፎና ደግፎ አለመያዝ፣ የቀድሞ አመራሮችን ተሞክሮዎች አለመጠቀምና ማኅበሩ የኢትዮጵያውያን ተቋም እንጂ የግል አለመሆኑን አለመለየት ናቸው።
ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት

Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now