አንኳሮች
- ክፍተትና ቅርርቦሽ
- ተግዳሮቶችና ትሩፋቶች
- የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተነሳሽነት
- የማኅበረሰብ አመራር
ፕሬዚደንት እሆናለሁ ብዬ አይደለም ወደ ቪክቶሪያ ኢትዮጵያውያን ማኅበር የተቀላቀልኩት፤ ሳላውቃቸው ለእኔ ውለታ ለዋሉልኝ ሰዎች ወሮታ ለመክፈል ነው።ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበር ፕሬዚደንት
ወደ ማኅበረሰብ አመራር በበጎ ፈቃደኝነት የገባሁት አገልግሎት ለመስጠት ነው። በተለይ ልጅ ከወለድኩ በኋላ ኢትዮጵያዊ ማንነትን ማስቀጠል ላይ ወሳኝነት እንዳለው ስለገባኝና ለልጆቻችን ኩራት የሚሆን ነገር ትቶ ማለፍ አለብኝ በሚል ነው።ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ፤ የኩዊንስላንድ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ






