ዶ/ር ዮናስ አዳዬ - በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ጸጥታ ጥናቶች መካነ ጥናት ዳይሬክተርና ነባር ፖለቲከኛ አቶ ሙሼ ሰሙ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሔደ ያለውን የለውጥ ሂደት ከሰሞነኛው ሁነት ጋር አሰናስለው አተያዮቻቸውን ያንጸባርቃሉ።
አንኳሮች
- “በዘር ላይ በተመሠረተ ፖለቲካ አንድነታችንን፣ ሰብዓዊነታችንንና የኢትዮያዊነት መለያ አብሮነታችንን አጥተናል… ከጎሣ ይልቅ ዜግነትን መሠረቱ ያደረገ ጥሩ የኢትዮጵያዊነት ማንነት መሠረት ተጥሏል።” ዶ/ር ዮናስ አዳዬ
- “ፈተናዎቻችን ብዙ ናቸው፤ ለውጡ ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ እየተጓዘ ነው። እንደ አገር ወደ ፊት ትልቅ ተስፋን እመለከታለሁ። በአንጻሩ በቂ አቅም መገንባት ላይ ካልተሠራ አገሪቱ ወደ አደጋ የማትሔድበት ምክንያት የለም ባይ ነኝ። ሆኖም ወደ ተስፋው አጋድላለሁ።” - አቶ ሙሼ ሰሙ
Share






