ዘውድና ሪፐብሊክ
አቶ ንብረት የዘውድ ሥርዓቱን የተካው የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ፤ ዘግይቶም ወደ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢሕዲሪ) የዞረው ሥርዓት ወዳጅና የማርክሲስት ሌኒንስት ርዕዮተ ዓለም አራማጅም አልነበሩም።
ከቶውንም የዘውዱ ሥርዓት በሪፐብሊክ የመተካት ጦስ ኢትዮጵያ ዛሬ ላለችበት የጎሣ ፖለቲካ ቀውስ መዳረግ አስባብ እንደሁ ያመላክታሉ።
በዘመነ ኃይለ ሥላሴ የነበረው ዲሞክራሲ ከዛሬው የአውስትራሊያ ዲሞክራሲ ይበልጥ እንደነበርም አመኔታቸውን ይገልጣሉ።
የዘመነ ደርግ መሬት ለአራሹ አዋጅም ለኢትዮጵያ ዋነኛ ቀውስ አንዱ ምክንያት ስለመሆኑና የባላባት ሥርዓት ኢትዮጵያን ያቆየ ነው በሚል አተያያቸውን ያጋራሉ።
በወቅቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ከተቃዋሚዎስ እስከ ገዢው ሰደድ ፓርቲና በኋልም የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ (ኢሠፓ) ያሉ ድርጅቶች በአባልነት እንዲቀላቀሉ ቢጠይቋቸውም ምላሻቸው እምቢታ ነበር።
ያም አስባብ ሆኖ በፀረ ማርክሲስት ሌኒንስት ተፈርጀው ከሥራ የኃላፊነት ደረጃቸው ዝቅ እንዲሉ ተደርጎ ከአዲስ አበባ ወደ ባሌ ለመላክ እንደበቁ ያወሳሉ።







