"የሰላም ድርድሩ ከከሸፈ አገራችን ውስጥ እስከ መቼውም ሊያባራ የማይችል የእርስ በርስ ጦርነት የሚያስከትለው ዕልቂት ሊመጣ ይችላል" አቶ ልዑል ፍሰሃ

Luel.jpg

Luel Fesseha. Source: SBS / L.Fesseha

አቶ ልዑል ፍሰሃ - በሜልተን ክፍለ ከተማ የሥራ ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ፣ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ - በብሪስበን ኩዊንስላንድ የደቡብ ማኅበረሰብ Mአዕከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ - በቪክቶሪያ AMES የሠፈራ ጉዳይ ሥራ አስኪያጅና ዶ/ር ተበጀ ሞላ - በዲከን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ጥናት ተመራማሪ፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል ሊካሔድ በዕሳቤ ስላለው የሰላም ድርድር አስፈላጊነት ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።


አንኳሮች
  • የድርድር ግቦች
  • የስኬት ትሩፋቶች
  • የክሽፈት መዘዞች

“ድርድሩ ከተሳካ በየትኛውም ወገን ላለ ሰው የሕይወትም የመንፈስም ትሩፋት ይኖረዋል፤ ካልተሳካ ማንም ተጠቃሚ አይሆንም። ምናልባትም የሚያተርፍ ቢኖር የኢትዮጵያን መውደቅ አሰፍስፈው ለሚጠብቁ ይሆናል።” ወ/ሮ ሰብለወርቅ አሰፋ

 ***

“ድርድሩ ካልተሳካ የምንመለሰው ወደ ጦርነት ነው። ተሳክቶ መፍትሔ ካገኘን ጦርነትና ውድመትን ያስቀርልናል።” አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ

 ***

“ድርድሩ እንዲሳካ የሚያደርጉ በርካታ ጉዳዮች አሉ። ድርድሩ የግድ መሳካት እንደሚኖርበት አስገዳጅ ሁኔታዎች አሉ። ያለውን ችግር በድርድር የመፍታት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። እንዲያም ሆኖ ድርድሩ ሳይሳካ ቢቀር እንደ ዳርፎርና ሶማሊያ ነው የምንሆነው።” ዶ/ር ተበጀ ሞላ


Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now