“ድርድሩ እንዲሳካ ለማድረግ የመንግሥትና የትግራይ ተደራዳሪዎች የቋንቋና የሚዲያ አጠቃቀማቸውን ከጦርነቱ ወቅት በተለየ አቅጣጫ ማለዘብ አለባቸው” አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ

D. Waqjira.jpg

Dabessa Waqjira. Source: SBS / D.Waqjira

አቶ ልዑል ፍሰሃ - በሜልተን ክፍለ ከተማ የሥራ ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ፣ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ - በብሪስበን - ኩዊንስላንድ የደቡብ ማኅበረሰብ ማዕከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ - በቪክቶሪያ AMES የሠፈራ ጉዳይ ሥራ አስኪያጅና ዶ/ር ተበጀ ሞላ - በዲከን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ጥናት ተመራማሪ፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል ሊካሔድ በዕሳቤ ስላለው የሰላም ድርድር አስፈላጊነት ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።


አንኳሮች
  • መደበኛ መሠረታዊ አገልግሎቶች አቅርቦት ለትግራይ
  • የክልልና ፌዴራል አስተዳደር በትግራይ
  • ጥርጣሬና አመኔታ

“ስጋቶቻችንን ይፋ እናድርግ። እንተማመን። ሁላችንም በዚህ ግፊት ውስጥ ከሄድን ውጤታማ አንሆንም። ውጤታማ የምንሆነው አንድ የጋራ አገር ይኑረን ብለን ዳግም ልብ የሚያደማ ነገር ውስጥ እንዳንገባ ከተማመን፣ ትዕቢታችንንና አልነካ ባይነታችንን ለጋራ ሰላም ስንል ስናስካ ብቻ ነው።” ወ/ሮ ሰብለወርቅ አሰፋ

***

“የትግራይ ሕዝብ የኢትዮጵያ ሕዝብ አካል ነው። በትግራይ ሕዝብ ላይ የሚደርስ በደል የሁላችንም ጥያቄ መሆን አለበት።” ዶ/ር ተበጀ ሞላ

 ***

“የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለፌዴራሉ መንግሥት ዕውቅናን መስጠት አለበት፤ የፌዴራል መንግሥቱ ለትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ዕውቅናን መስጠት አለበት። ዕውቅና ካልተሰጣጡ ድርድሩ ዋጋ የለውም።” አቶ ልዑል ፍሰሃ


Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now